በዩኒቨርሲቲ ሕይወት ዙሪያና በፍቅር ታሪክ ላይ በሚያተኩረው ሰመመን በሚባለው መጽሐፋቸው በብዙዎች ዘንድ የታወቁት ሲሳይ ንጉሡ፣ ጉዞው፣ ግርዶሽ፣ የቅናት ዛር የተባሉ ረጃጅም ልብወለዶች አሏቸው፡፡ ጉዞው የሚለውን ኖቬላ ጨምሮ ሌሎች አጫጭር ልብወለዶችን ጽፈዋል፡፡ ከኢትዮጵያ ሥነ ጥበባትና መገናኛ ብዙኃን ሽልማት በሥነ ጽሑፍ ዘርፍ በ 1991 ዓ.ም. ተሸላሚም ሆነዋል፡፡ ቀደም ባሉት ጊዜያት የደራሲያን ማኀበር ዋና ጸሐፊ በመሆን አገልግለዋል፡፡




